አበራ ጀምበሬ በቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሀገር ነሐሴ ፳፯/፲፱፳ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞው ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ገብተው አጠናቅቀዋል። ከዚያም በማስከተል በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ገብተው የቤ.ኤ እና የኤል.ኤል.ቢ BA LLB ዲግሪዎቻቸውን ወስደዋል፡፡
አበራ ጀምበሬ “ስለጋብቻችሁ”፣ “የቀ.ኃ.ሥ. በጎ አድራጎት ድርጅት መመሥረት”፣ “አባ ኮስትር”፣ “ብቸኛው ሰው”፣ “አባ ገስጥ”፣ “የእሥር ቤቱ አበሳ” በሚሉ ርዕሶች መጻሕፍት አሳትመው ለአንባቢያን ያበረከቱ ሲሆን ገና ያልታተሙ ሥራዎችም አሏቸው፡፡ |