ደራሲያን በፊደል ማውጫ
   
 
 
ነጋሽ ገብረማርያም Negash Gebremariam
የደራሲው ሥራዎች
1.   FE(ልብወለድ)
2.   የድል አጥቢያ አርበኞች(ተውኔት)

ስለደራሲው በጥቂቱ
ነጋሽ ገ/ማርያም በ፲፱፲፯ ዓ.ም. በሐረርጌ ጠ/ግዛት በጨርጨር አውራጃ በሀብሮ ወረዳ ልዩ ስሟ መቻራ በምትባል አካባቢ ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በአካባቢያቸው የባህላዊ ትምህርት ተከታትለዋል።

ከጣሊያን ወረራ በኋላ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ጎልቶ መታየት በመጀመሩ ጣሊያኖችን በብዙ ነገሮች ማውገዝና መቃወም ተጀመረ፡፡ እነሱም እንደ ሲጋራ ማጨስ፣ ሴተኛ አዳሪነትንና የመሳሰሉት ነበሩ፡፡ ነጋሽ ይህን በተመለከተ ሴተኛ አዳሪነትና ምንም እንኳን በጣሊያኖች ጊዜ ይፋ በሆነ መንገድ ቢታይም ከዚያ በፊት እንደነበረም “ሴተኛ አዳሪ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ገልጸውታል፡፡

ነጋሽ ገ/ማርያም ችሎታቸውን ያሳዩት “ሴተኛ አዳሪ” የተሰኘ ልብወለድ መጽሐፋቸውን በጻፉበት ጊዜ ነበር፡፡ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ድራማዎች ውስጥ “የአዛውንቶች ክበብ” እና “የድል አጥቢያ አርበኞች” ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ምንጭ: የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
   
   
       
 
   
     
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
     
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com