ቀኛዝማች ታደሰ ዘወልዴ በ1895 ዓ.ም ተወለዱ። ዘመናዊ ትምህርታቸውን ዳግማዊ ምኒሊክ ትምህርተ ቤት ተማሩ።
በ1919 ዓ.ም. ወደ ግብፅ አገር ሄደው ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ከተመረጡት ሃያ አንድ ተማሪዎች መካከል አንዱ ነበሩ። በዚህም መሠረት እስክንድሪያ ከተማ ሊሴ ፍራንሴስ ትምህርት ቤት ገቡ።
ከዚያም ወደ ፈረንሳይ አገር ተሻግረው የቴሌኮሚኒኬሽን ልዩ ትምህርት ሲማሩ ቆዩ።
ኾኖም በ1928 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ላይ የፋሺስት ወረራ ስለደረሰ የክተቱን አዋጅ በወዶዘማችነት በመቀበል ከፓሪስ ወደ ማይጨው ዘመቱ። |