[
ዋና ገጽ
|
ስለኛ
|
አስተያየት
|
አድራሻችን
]
ታሪክ
|
ምርምርና ጥናት
|
ልቦለድ
|
ግጥምና ቅኔ
|
ተውኔት
|
ትምህርት
|
ፍልስፍና
|
ተረቶችና ቀልዶች
|
ትርጉም
|
ወግ
|
መንፈሳዊ ድርሰቶች
|
መዛግብተ-ቃላት
የኢትዮጵያ ደራሲያን በፊደል ማውጫ
አ
በ
ቨ
ገ
ደ
ጀ
ሀ
ወ
ዘ
ዠ
ሐ
ኀ
ጠ
ጨ
የ
ከ
ኸ
ለ
መ
ነ
ኘ
ሠ
ዐ
ፈ
ጸ
ፀ
ቀ
ረ
ሰ
ሸ
ተ
ቸ
ጰ
ፐ
ወደ ዋና ገጽ
ለማ ፈይሳ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
የተወለዱት ላዛሪስት ትምህርት ቤት አካባቢ ነጋድራስ ጨርቆስ ሰፈር በ፲፱፲፱ ዓ.ም. ነው፡፡ በሕጻንነታቸው ወላጆቻቸው ስለሞቱ ያደጉት ከአጎታቸው ቤት ነው። የመጀመሪያ ትምህርታቸውን የተከታተሉት ላዛሪስት ሚሲዮን ትምህርት ቤት ሲሆን በጠላት ወረራ ጊዜ ጣሊያን ት/ቤት ገብተው በጣሊያንኛ ቋንቋ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ ፋሽስት ኢጣሊያ ተሸንፎ ከተባረረ በኋላ ወደ እንድብር በመሄድ ለሁለት ዓመታት በፈረንሳይኛ ቋንቋ፤ ለሦስት ዓመታት በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ ቋንቋ በመማር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከመጀመሪያዎቹ የሕግ ምሩቃን መካከል በከፍተኛ ማዕረግ በመመረቅ የመጀመሪያው ሰው ናቸው፡፡ በንግድ ሕግ የዶክተርነት የክብር ዲግሪ ከሎንዶን ኢንስቲትዩት አግኝተዋል፡፡
“ፒኖኪዮ” በሚል ርዕስ በጣሊያንኛ ቋንቋ የተጻፈውን መጽሐፍ “አፍንጮ” በሚል ርዕስ “ላፎንቴን” ተረትና ምሳሌዎች የተካተቱበትን “ኮሬ” የተባለውን መጽሐፍ ከጣሊያንኛ “ልባሙ ልጅ” በሚል ርዕስ በሦስት ክፍል ተተርጉመዋል፡፡ “አኒማል ፋርም” የሚለውን የእንግሊዝኛ መጽሐፍ “የእንስሳት ዕድር” በማለት ተርጉመው ለአንባቢያን አቅርበዋል፡፡ ከድርሰት ሥራ ወይም ከትርጉም ውጭ ልኖር አልችልም የሚሉት አቶ ለማ አማርኛ፣ ግዕዝና ጉራጊኛ፤ ከውጭ ቋንቋዎች እንግሊዝኛና ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛና ላቲን ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡
ለማ ፈይሳ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ሰርተዋል፡፡ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ትልቅ ደረጃ እንዲደርስ መሠረት የጣሉት እሳቸው ናቸው ማለት ይቻላል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
የተወለዱት ላዛሪስት ትምህርት ቤት አካባቢ ነጋድራስ ጨርቆስ ሰፈር በ፲፱፲፱ ዓ.ም. ነው፡፡ በሕጻንነታቸው ወላጆቻቸው ስለሞቱ ያደጉት ከአጎታቸው ቤት ነው።
ሉሌ መላኩ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ላቀው ደስታ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዶ/ር ላጵሶ ጌ.ድሌቦ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ ፕሮፌሰር በከንባታና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ሐበሌ ግንቦት ፲፪ ቀን ፲፱፻፴ ዓ.ም. ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቢቾ ሆሣዕና ሚሽን ት/ቤትና በመንግሥት ትምህርት ቤት ሲከታተሉ ቆይተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዓጼ ገላውዴዎስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በባይብል አካዳሚ ናዝሬት ተምረዋል፡፡ ከዚያም በአሜሪካ ኮሙኒቲ ኮሌጅ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው በኀብረተሰብ ታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል፡፡ ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲም በአፍሪካ ታሪክ ጥናት የኤም.ኤ ዲግሪያቸውን፣ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካና በአውሮፖ ታሪክና በፍልስፍና የፒ.ኤች.ዲ ዲግሪያቸውን ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ ወስደዋል፡፡
ላጵሶ ጌታ ድሌቦ “የኢትዮጵያ የገባር ሥርዓትና ጅምር ካፒታሊዝም፣ 1ኛና 2ኛ የታሪክ መጻሕፍት”፣ “የኢትዮጵያ ረጅም የሕዝብና የመንግሥት ታሪክ 1ኛ መጽሐፍ”፣ “የቀይ ባሕርና የአባይ ሸለቆ ሚና፣ የምፅዋ ሲምፖሲየም-1974”፣ “የኢትዮጵያ የመከራ ሥርዓትና የኤርትራ ጥያቄ፣ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መጽሐፍ” ና ሌሎች በርካታ የታሪክ መጻሕፍት አሳትመው ለአንባብያን አቅርበዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮጵያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ ፕሮፌሰር በከንባታና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ሐበሌ ግንቦት ፲፪ ቀን ፲፱፻፴ ዓ.ም. ተወለዱ።
[1500 - 1530]
ዐፄ ልብነ ድንግል
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ልሳነወርቅ ገብረኢየሱስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
መጻሕፍት ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ
ይጫኑ
ተመዝግበው ከሆነ እዚህ
ይጫኑ
[
ታሪክ
|
ምርምርና ጥናት
|
ልቦለድ
|
ግጥምና ቅኔ
|
ተውኔት
|
ትምህርት
|
ፍልስፍና
|
ተረቶችና ቀልዶች
|
ትርጉም
|
ቋንቋ
|
ወግ
|
መንፈሳዊ ድርሰቶች
|
መዛግብተ-ቃላት
]
[
ዋና ገጽ
|
ስለኛ
|
አስተያየት
|
አድራሻችን
]
መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com